Fana: At a Speed of Life!

አየር መንገዱ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ወደ 80 ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች ሲያደርግ የነበረውን በረራ አቋረጠ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 20 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ወደ 80 ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች ሲያደርግ የነበረውን በረራ ከዛሬ ጀምሮ ማቋረጡን አስታወቀ።

አየር መንገዱ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚደረጉ የካርጎ( የእቃ ማመላለሻ) በራሮች ግን ይቀጥላሉ ብሏል።

የሀገር ውስጥ ገበያ 50 በመቶ መቀነሱን ያስታወቀው አየር መንገዱ በሀገር ውስጥ የሚያደርጋቸው በረራዎች እንደሚቀጥሉ ገልጿል።

አየር መንገዱ በመግለጫው የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑንም አስታውቋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.