Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮ አፍሪካ የአሰግድ ተስፋዬ የመታሰቢያ ውድድር አሸናፊ ሆነ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 12 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሰግድ ተስፋዬ የመታሰቢያ ውድድር በኢትዮ አፍሪካ የእግር ኳስ ቡድን አሸናፊነት ተጠናቀቀ፡፡

የፍጻሜ ጨዋታው በኢትዮ አፍሪካ እና አበበ ቢቂላ ቡድኖች መካከል የተደረገ ሲሆን፥ መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜው አንድ ተጠናቋል፡፡

በመለያ ፍጹም ቅጣት ምት ኢትዮ አፍሪካ 5 ለ 4 አሸናፊ ሆኗል።

ውድድሩ መጠናቀቁን ተከትሎም የውድድሩ ኮከቦች የተመረጡ ሲሆን፥ ቢኒያም ኃይሌ ከኢትዮ አፍሪካ ኮከብ ተጫዋች፣ ሚራጅ ነስረዲ ከኢትዮ አፍሪካ በአምስት ጎል ኮከብ ጎል አግቢ፣ ሳሙኤል ዳኜ ከኢትዮ አፍሪካ ኮከብ አሰልጣኝ እንዲሁም ውብሸት ደሳለኝ ከኢትዮ አፍሪካ ኮከብ ግብ ጠባቂ በመሆን ተመርጠዋል፡፡

ኮተቤ እግርኳስ ማኅበር ደግሞ የስፖርታዊ ጨዋነት አሸናፊ መሆኑን የሶከር ኢትዮጵያ ዘገባ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.