Fana: At a Speed of Life!

ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ  የኩዌት ሊግ ውድድሮችን ለመምራት ወደ ስፍራው ያቀናሉ

 

አዲስ አበባ፣ ህዳር 23፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ  በኩዌት ሊግ ውድድሮችን ለመምራት መመረጣቸውን ተከትሎ ዛሬ ወደ ስፍራው ያቀናሉ፡፡

 

የኩዌት እግር ኳስ ማህበር ሰሞኑን ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በጻፈው ደብዳቤ÷  ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ ከህዳር 2 – 13 በኩዌት ኤስ ቲ ሲፕሪሜሪሊግ  የሚደረጉ ጨዋታዎችን በዋና ዳኝነት እንዲመሩ በጠየቁት መሰረት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥያቄዉን በመቀበሉ ነው ወደ ስፍራው የሚያቀኑት፡፡

 

በዚሁ መሰረት ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ ዛሬ ማምሻውን ወደ ስፍራው እንደሚያመሩ  ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ያኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

 

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.