Fana: At a Speed of Life!

ኢጋድ 2 ሚሊየን ዶላር የሚጠጋ ለኮቪድ መከላከያ የሚውሉ ቁሳቁስ ለጅቡቲ አበረከተ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 12፣ 2013 (ኤፍቢሲ) የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) 1 ነጥብ 9 ሚሊየን ዶላር ለኮቪድ መከላከያ የሚውል ቁሳቁስ ለጅቡቲ አበረከተ፡፡

የኢጋድ ዋና ፀሃፊ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ኢጋድ አምቡላንስን ጨምሮ የተለያዩ የህክምና ቁሳቁሶችን ለጅቡቲ ድጋፍ ማድረጉን በፌስቡክ ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም በኢጋድ አባል ሃገራት መካከል ተመሳሳይ ድጋፍ እንደሚደረግም ነው ያስታወቁት፡፡

አክለውም በወረርሽኙ የተጎዱ የማህበረሰብ ክፍሎችን በሚደረገው ጥረት የኢጋድና የአውሮፓ ህብረት የጋራ ጥረት ፍሬ ማፍራቱን ገልጸዋል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤

ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ

ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.