Fana: At a Speed of Life!

“እኔም ለደሴ እሮጣለሁ” ሕዝባዊ ሩጫ በደሴ ከተማ ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 21 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የደሴ ከተማ እግር ኳስ ክለብን ለመደገፍ “እኔም ለደሴ እሮጣለሁ” በሚል መሪ ቃል ሕዝባዊ ሩጫ በደሴ ከተማ ተካሂዷል፡፡

የደሴ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎች ማኅበር ባዘጋጀው ሕዝባዊ ሩጫ ላይ በርካታ የከተማዋ ነዋሪዎችና ከተለያዩ አካባቢዎች የታደሙ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡

ክለቡን ለማገዝ ከ4ሺህ በላይ ቲሸርቶች ታትመው ለሽያጭ መቅረባቸውን አብመድ ዘግቧል፡፡

የደሴ ከተማ እግር ኳስ ክለብ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ እየተወዳደረ የሚገኝ ሲሆን በዚህ ዓመት በሊጉ በመጀመሪያው ዙር ውድድር በምድብ አንድ በ16 ነጥብ 2ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.