Fana: At a Speed of Life!

ከትግራይ ልዩ ኃይል የመጡ የሽብር ቡድኑ አባላት በቁጥጥር ሥር ዋሉ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 25 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከትግራይ ልዩ ኃይል የመጡ የሽብር ቡድኑ አባላት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።

የሽብር ቡድኑ ሁለት አባላት አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቱሉ ዲምቱ አካባቢ 11:00 ሰዓት ላይ በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ መደረጉንም ነው አስተዳደሩ ያስታወቀው።

በቁጥጥር ሥር የዋሉት ዘመን ገ/እግዚአብሔር (የጥበቃ መምሪያ አባል የነበረ የፈንጂ ባለሙያ) እንዲሁም ገ/ኪዳን ገ/ጻድቅ የልዩ ኃይሉ አባል መሆናቸውን ገልጿል።

አሁን ላይም በሽብር ቡድኑ አባላት ላይ ከፌደራል ፖሊስ ጋር በመሆን ምርመራ መጀመሩንም አስታውቋል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.