Fana: At a Speed of Life!

ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ሶስት ምክትል ፕሬዚዳንቶቹን ከስራ አገደ

አዲስ አበባ ፣ ጥር 8 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ሶስት ምክትል ፕሬዚዳንቶቹን ከስራ ማገዱን አስታወቀ።

በዩኒቨርሲቲው የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ተፈራ አስናቀ ሶስቱ ምክትል ፕሬዚዳንቶች የታገዱት በዩኒቨርሲቲው ሴኔት ውሳኔ መሰረት መሆኑን ተናግረዋል።

የመታገዳቸው ዝርዝር ምክንያት ለጊዜው አለመገለጹን ከኢዜአ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ዩኒቨርሲቲው ካለፈው ህዳር ወር መጨረሻ ጀምሮ በመማር ማስተማር ስራው ላይ አለመረጋጋት ገጥሞት መቆየቱ ይታወቃል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.