Fana: At a Speed of Life!

ዋልያዎቹ የ2023 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታቸውን ግንቦት 25 ቀን ይጀምራሉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ጨዋታ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ የሚያደርግባቸው ቀናት ይፋ ሆነዋል፡፡
የ2023 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ጨዋታዎች በዚህ ወር መካሄድ የሚጀምሩ ሲሆን÷ ኢትዮጵያ 2 ጨዋታዎችን የምታደርግበት ቀናት ታውቀዋል፡፡
በምድብ መ ከግብፅ፣ ጊኒ እና ማላዊ ጋር የተደለደለችው ኢትዮጵያ÷ የምድቡን የመጀመሪያ ጨዋታ ከማላዊ ብሄራዊ ቡድን ጋር ግንቦት 25 ቀን 2014 ታደርጋለች፡፡
ሁለተኛ ጨዋታዋን ደግሞ ግንቦት 29 ከግብፅ ጋር የምታደርግ መሆኑን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.