Fana: At a Speed of Life!

የህወሓት ጁንታን ጭካኔ የሚያወግዙ ሰልፎች ተካሄዱ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 27፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የህወሓት ጁንታውን ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት የሚያወግዙ ሰልፎች በማይካድራ፣ ቆቦ፣ አላማጣ ተካሄዱ።

የሀገር መከላከያ ሰራዊት በትግራይ ክልል እያከናወነ ያለውን ህግ የማስከበር ዘመቻ እንደሚደግፉ አሳውቀዋል።

ሰልፈኞቹ የትግራይ ህዝብ መልካም ወንድም እና እህት መሆኑን ገልጸዋል።

ከሀዲው የህወሓት ቡድን ለመልካሙ የትግራይ ህዝብም ጠላት ነው ብለዋል ሰልፈኞቹ።

በሰሜን እዝ ላይ የተፈፀመው ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት ታሪክ መቼም የማይዘነጋው ክህደት ነው ብለዋል፡፡

መንግስት ይህንን አረመኔያዊ ድርጊት የፈፀሙ አካላትን ተከታትሎ ተገቢውን ህጋዊ እርምጃ ሊወስድባቸው ይገባል ሲሉም ሀሳባቸውን ገልጸዋል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤

ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ

ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.