የህዳሴው ግድብ የልማት እንጂ ሌላ ጉዳይ የለውም-አብዱልፈታህ አል-ሲሲ
ፕሬዚዳንቱ ኢትዮጵያውያንን በልማት ማገዝ እንሻለን፤ “ይህ የሚሆነው ግን የውሃ ድርሻችን የማይነካ ከሆነ ነው” ብለዋል፡፡
አል ሲሲ “በዓለም ዓቀፍ ህግ አግባብ ተስማምተን በሰላም እና ብልጽግና እንኑር” ሲሉም ለኢትዮጵያና ለሱዳን ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በንግግራቸው የውሃ ጉዳይና ብሄራዊ ጥቅማቸውን ማስከበር የማይታለፍ ቀይ መስመር መሆኑንም አንስተዋል፡፡
አያይዘውም የግድቡን ወደ ፀጥታው ምክር ቤት የወሰዱት በጉዳዩ ዙሪያ ዓለም ዓቀፉን ማህበረሰብ ትኩረት ለማግኘት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ሃገራቸው ብሄራዊ ጥቅሟን ለማስከበር ብዙ አማራጭ እንዳላት ያነሱት ፕሬዚዳንቱ አማራጮቹንም እንደ አስፈላጊቱ መጠቀም እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
“ግብጽ የኢትዮያውያን ብሎም የአፍሪካውያን ህይወት እንዲሻሻል ድጋፍ ማድረግ ትችላለች፤ ይህ ግን የግብጽ የውሃ ድርሻ የማይነካ ከሆነ ብቻ ነው” ሲሉም ተደምጠዋል፡፡
ይህን ተፈጻሚ ለማድረግ ሰጥቶ የመቀበል መርህን እንደሚከተሉም አንስተዋል፤ ከዚህ አንጻርም ያቀረቡት ጥሪ ጤናማ እንዳልሆነ ማሳያ ነው፡፡