Fana: At a Speed of Life!

የመዉሊድ በዓል በተለያዩ ሀገራት እየተከበረ ነዉ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) 1 ሺህ 496ኛው የመውሊድ በዓል በተለያዩ የዓለም ሃገራት እየተከበረ ይገኛል፡፡

በዓሉ በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ እየተከበረ የሚገኝ ሲሆን÷ የነብዩ ሙሃመድ(ሰ.ዐ.ወ) ውልደትን በማሰብ ተከብሮ ይውላል፡፡

ኢትዮጵያን ጨምሮ ግብጽ፣ ሱዳን፣ የመን እና ናይጀሪያ በዓሉን ከሚያከብሩት የአፍሪካ ሃገራት መካከል ይጠቀሳሉ፡፡

በተጨማሪም በዓሉ በተለያዩ የአዉሮፓ እና እስያ ሃገራት በመከበር ላይ ነው፡፡

አዉስትራሊያ፣ ሩሲያ፣ ፓኪስታን፣ ባንግላዲሽ እና ፊሊፒንስ በዓሉን ከሚያከብሩ ሃገራት መካከል ተጠቃሽ ናቸው፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.