Fana: At a Speed of Life!

የምክንያታዊ ወጣት የውይይትና የሙግት መድረክ በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ ጥር 8 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የምክንያታዊ ወጣት የውይይትና የሙግት መድረክ በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ እየተካሄደ ነው፡፡

በመድረኩ ከከተሞቹ የተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ ምሁራን ወጣቶች እየተሳተፋበት ሲሆን የሀገረ መንግስት ግንባታና የወጣቱ ሚና በሚል ርዕስ የተሰናዳ መሆኑ በመድረኮቹ ተገልጿል።

በመድረኩ ምሁራን ወጣቶች ምክንያታዊ ሆነው የሃገር ግንባታ ላይ አሻራቸውን ለማሳረፍ ምክንያታዊ እና በእውቀት ላይ የተመሰረተ ሙግት እያደረጉ ይገኛሉ።

በብልጽግና ወጣቶች ሊግ እየተሰናዳ የሚገኘውና በመላ ሃገሪቱ እየተካሄደ ባለው መድረክ ጥናታዊ ፅሁፍ ቀርቡ ውይይት እየደተረገበት ይገኛል፡፡

በመድረኩ የዩኒቨርሲቲዎች እና ኮሌጆች ምሁራን፣ የዓለም አቀፍ ድርጅት ሰራተኞች፣ ከመንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት እንዲሁም በርካታ የከተማዋ ወጣቶች ተሳታፊዎች ናቸው፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.