የሱዳን መንግስት ከተቃዋሚወች ጋር የሰላም ስምምነት ተፈራረመ
አዲስ አበባ ፣ ጥር 16 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የሱዳን መንግስት ከተቃዋሚዎች ጋር የሰላም ስምምነት ተፈራረመ።
ስምምነቱ ከሰሜኑ የሱዳን ህዝቦች ነፃ አውጭ ንቅናቄ (ኤስ ፒ ኤል ኤም፤ ኤን) ጋር የተፈረመ ነው ተብሏል።
የአሁኑ ስምምነት በቀጠናው የተያዘው የሰላም እቅድ አካል መሆኑም ነው የተነገረው።
ቡድኑ ከፈረንጆቹ 2011 ጀምሮ በትጥቅ ትግል ላይ ቆይቷል።
ኤስ ፒ ኤል ኤም፤ ኤን የብሉ ናይል እና ደቡብ ኮርዶፋ አካባቢዎችን የማስተዳደር እቅድ እንዳለው ይነገራል።
ምንጭ ፡- አልጀዚራ