Fana: At a Speed of Life!

የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ በየደረጃው ካሉ የፓርቲው አመራሮች ጋር ምክክር እያካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 30 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ከሁሉም የክልሉ የገጠር ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች የፓርቲው አመራሮች በተገኙበት በሀዋሳ ከተማ የምክክር መድረክ እየተከናወነ ይገኛል።
የውይይት መድረኩም ሀገራዊ ወቅታዊ ሁኔታ፣ የ2013 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የአፈፃፀም ግምገማ፣ የ2013 ዓ.ም በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይትና የአሠራርና አደረጃጀት መመሪያ ላይ ትኩረት ማድረጉን ከክልሉ ብልፅግና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት እና የማህበራዊ ሚዲያ ዘርፍ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

#FBC

የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.