የሶማሊላንድ ምክትል ፕሬዝዳንት ጅግጅጋ ገቡ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሊላንድ ም/ፕሬዝዳንት አብዱረህማን አብዱላሂ ሰይሊኢ የተመራው ልዑክ ዛሬ ከሰዓት ጅግጅጋ ገባ።
ለምክትል ፕሬዝዳንቱና ልዑካቸው በቶጎጫሌ ከተማ የሶማሌ ክልል ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ሀላፊዎች ደማቅ አቀባበል አድርገዋል።
የሶማሊላንድ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱረህማን አብዱላሂ ሰይሊኢ እና ልዑካቸው በነገው ዕለት በጅግጅጋ ከተማ የሚመሠረተው አዲሱ የሶማሌ ክልል የመንግሥት ምስረታ ላይ እንደሚሳተፉ ከሶማሌ ክልል ብዙሃን መገናኛ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!