Fana: At a Speed of Life!

የሶማሊያ ፕሬዚዳንት የጠቅላይ ሚኒስትሩን ስልጣን አገዱ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሊያ ፕሬዚደንት ሞሀመድ አብዱላሂ ፋርማጆ የጠቅላይ ሚኒስትር ሞሀመድ ሁሴን ሮብልን ባለስልጣናትን የመሾም እና የመሻር ስልጣን አግጃለሁ ብለዋል፡፡

የሶማሊያ ፕሬዚዳንት የሆኑት አብዱላሂ ሞሃመድ(ፋርማጆ) የሃገሪቱንጠቅላይ ሚኒስትር ስልጣን አግደዋል፡፡

የእገዳ ውሳኔውም የደህንነት መስሪያ ቤት ሰራተኛ ኢክራም ታህሊል ፋራህ ግልጽ ባልሆነ ምክንያት መሰወርን ተከትሎ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡

በሶማሊያ ከፍተኛ አመራሮች መካከል ያለው መከፋፈል መጪዎቹ ምርጫዎች ላይ ስጋት እንደሚጭር እየተዘገበ ነው።

ምንጭ፡- ቢቢሲ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.