Fana: At a Speed of Life!

የባህልና ቱሪዝም ዘርፍ ለህዝቦች የእርስ በእርስ ግንኙነት መጠናከር ሚናው ከፍ እንዲል መደረግ አለበት – ዶ/ር ሂሩት ካሳው  

 

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 9 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)- የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የ2013 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በሐረር ከተማ እየቀረበ ይገኛል፡፡

የባህልና ቱሪዝም ሚንስትር ዶ/ር ሂሩት ካሳው ለዘርፉ እድገት የልምድ ልውውጥ በማድረግ ሴክተሩ የህዝቦች እርስ በእርስ ግንኙነትን በማጠናከር በሀገራችን ፍቅር፣ ሰላም እና አንድነት እንዲፈጠር በጋራ  ለመስራት የምናቅድበት ጊዜ ነው ብለዋል፡፡

የሀረሪ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ዲኒ ረመዳን ፣ክልሎች ዕርስ በዕርስ የልምድ ልውውጥ የምናደርግበት እንዲሁም ዘርፉ ለህዝባችን አንድነትና ሰላም ያለውን ድርሻ ለማሳደግ በትብብር መስራት ይገባናል ብለዋል፡፡

የ9 ወራት እቅደ አፈፃፀም ሪፖርት እና የቀጣይ ቀሪ ወራት እቅድ የሚቀርብበት መድረክ መሆኑን ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.