የቤኒሻንጉል ክልል የትግራይ ክልልን መልሶ ለማቋቋም የ15 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 18፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት የትግራይ ክልልን መልሶ ለማቋቋም የሚውል 15 ሚሊዮን ብር እና የ1 አምቡላንስ ድጋፍ አደርጓል።
እንደ ሀገር ከጁንታው መወገድ በኋላ የትግራይ ክልልን መልሶ-ለማቋቋም በመንግስት እየተሠራ ያለው ሥራ መልካምና የሚደገፍ መሆኑንም የክልሉ መንግስት ይገልጻል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ወደፊትም የትግራይ ክልልን መልሶ-ለማቋቋም የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!