Fana: At a Speed of Life!

የብሔራዊ ጤና መረጃ ስርዓት አስተባባሪ ኮሚቴ በኢትዮጵያ የጤና መረጃ ላይ በተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ውይይት አካሄደ

አዲስ አበባ ፣ህዳር 16 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)ከመንግስትና ከአጋር ድርጅቶች የተዋቀረው የብሔራዊ ጤና መረጃ ስርዓት አስተባባሪ ኮሚቴ በኢትዮጵያ የጤና መረጃ አብዮት ላይ እስካሁን የተሰሩ ስራዎችን እንዲሁም የታዩ ክፍተቶች እና ተግዳሮቶች ዙሪያ ውይይት አካሄደ።
የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ላይ ÷በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ጥራት እንዲሁም መረጃን በሁሉም ደረጃዎች መጠቀም የጤና ስርዓትን ለማሻሻል መሰረት ነው ብለዋል።
ዶክተር ሊያ አያይዘውም እነዚህን ቁልፍ ጉዳዮች ወደፊት ለማስኬድ የጤና መረጃ አስተዳደር ስርዓትን ለማጠናከር በውይይቱ ተስማምተናልም ነው ያሉት፡፡
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.