Fana: At a Speed of Life!

ቻይና እና አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ላይ በትብብር ለመሥራት ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና እና አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል በጋራ ለመስራት ተስማሙ።

የአየር ንብረት ለውጥ በተፈጥሯዊ ሥነ-ምህዳር እንዲሁም በማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያደረሰ መሆኑ ይነገራል።

በመሆኑም በዳካር በተካሄደው 8ኛው የቻይና – አፍሪካ የትብብር የሚኒስትሮች ፎረም ላይ÷ ቻይና እና አፍሪካ በጉዳዩ ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የትብብር ሰነድ አዘጋጅተዋል፡፡

የቻይና አፍሪካ ትብብር ጉባኤ በፈረንጆቹ 2000 መካሄድ የጀመረ ሲሆን÷ በሥነ – ምህዳርና አካባቢ ጥበቃ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ያደረገ መርሃ ግብር ነው፡፡

በደን እና በሥነ-ምህዳር ጥበቃ፣ ዘላቂ የተፈጥሮ ሐብት አጠቃቀም እና የኃይል አቅርቦት፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የታዳሽ ኃይል አቅርቦት፣ በአካባቢ መሠረተ – ልማት ግንባታ፣ በንጹህ ውሃ አቅርቦት፣ በዱር እንስሳት ጥበቃ እንዲሁም በርሃማነትን በመከላከል ላይ ጉባኤው ውይይት ያደረገባቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን የዘገበው ሲጂቲ ኤን ነው፡፡

 

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.