Fana: At a Speed of Life!

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ በኢትዮጵያ ጉብኝት እያደረጉ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ ትናንት ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል።

ፖምፒዮ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው አቀባበል አድርገውላቸዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዛሬ ከአቶ ገዱ አንዳርጋቸው ጋር የሁለቱን አገሮች የሁለትዮሽ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ያደርጋሉ።

በተጨማሪም ከኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እና ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ጋር እንደሚወያዩ የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.