Fana: At a Speed of Life!

የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ሙያተኞችን ለማሰልጠን የድጋፍ ሥምምነት ተፈረመ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የአሜሪካ ተራድዖ ድርጅት እና ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ሙያተኞችን ለማሰልጠን የድጋፍ ሥምምነት ተፈራረሙ።

ሥምምነቱን የዩ ኤስ አይ ዲ ዳይሬክተር ሺን ጆንስ እና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ተሥፋዬ ሽፈራው (ዶ/ር) ተፈራርመዋል።

የድጋፍ ስምምነቱ 7 ነጥብ 7 ሚሊየን ዶላር ሲሆን፥ ድጋፉ ቀጣዩን ትውልድ በአደጋ ሥጋት አመራር ለማሠልጠን እና ባለሙያዎችን ለማፍራት የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡

ቀደም ሲል በኢትዮጵያ የአሜሪካ ተራድዖ ድርጅት መዋዕለ-ንዋይ ዕውን የሆነው “ፊድ ዘ ፊውቸር ኢትዮጵያ” የተሰኘው መርሐ-ግብር ላለፉት ሁለት አሥርት ዓመታት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሲተገበር መቆየቱን ዩ ኤስ ኤይድ በኢትዮጵያ በመረጃው አመላክቷል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.