Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎትን የዲጂታል አሰራር የማሻሻል ስራ  ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 9 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከጀርመን የኢኮኖሚ ጉዳዮች  እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር የኢትዮጵያ ፖስታ አገልገሎት የዲጂታል አሰራርን  ለማዘመን በጋር ለመስራት ተስማምተዋል።

በስምምነቱ መሰረት የጀርመን የኢኮኖሚ ጉዳዮች  እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ድጋፎችን ያደርጋል ነው የተባለው።

በሁለቱ ሚኒስቴር መስሪያቤቶች በተደረሰው ስምምነት መሰረት የድጋፍ ስራው በየካቲት ወር መጀመሪያ እንደሚጀመርም ነው የተገለጸው።

በውይይቱ ላይ ከሁለቱ ሚኒስቴር መስሪያቤት  የስራ ሃላፊዎች ፣የጀረመን ፖስታ አገልገሎት እና የኢትዮጵያ ፖስታ አገልገሎት ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

ኢትዮጵያ ያፀደቀችው የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን  ስትራቴጂ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ አንዱ የኢኮሜርስ አገልግሎትን ማስፋፋትመሆኑም ተመላክቷል።

ኢኮሜርስን ለመተግበር ደግሞ ዘመናዊ የፖስታ አሰራር ወሳኝ ድርሻ አለውም ነው የተባለው፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎትን የዲጂታል አሰራርን የማሻሻል ስራ ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂው ስኬት ወሳኝ ድርሻ አለው መባሉን ከኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.