Fana: At a Speed of Life!

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከኤች ኤንድ ኤም ተወካዮች ጋር በመቐለ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ዙሪያ ተወያየ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሳንዶካን ደበበ ከኤች ኤንድ ኤም ተወካዮች ጋር ተወያዩ፡፡

ውይይቱ በመቐለ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ነበር ተብሏል፡፡

ሁለቱ ወገኖች ለዘርፉ እድገት እና የተቀመጡ ሁሉን አቀፍ የልማት ግቦችን ለማሳካት በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል፡፡

ኤች ኤንድ ኤም በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ኢንዱስትሪ ልማት ለኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ አጋር ነው፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.