Fana: At a Speed of Life!

የኦሮሚያ ክልል የስራ ኃላፊዎች በአዳማ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 19፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኦሮሚያ ክልል የስራ ኃላፊዎች በአዳማ ከተማ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ፡፡

በኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪ ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ የተመራ ልዑክ በአዳማ ከተማ ተገንብተው ለአገልግሎት የበቁ እና በግንባታ ላይ ያሉ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝቱም የኦሮሚያ ክልል የሴክተር መስሪያ ቤቶች የስራ ኃላፊዎች እና የተለያዩ ከተሞች ከንቲባዎች ተሳትፈዋል፡፡

ልዑኩ የአዳማ ከተማ ከንቲባ ፅ/ቤት ህንፃን በመመረቅ በቴክኖሎጂ የታገዙ የአገልግሎት አሰጣጥ ስራዎችን ጎብኝተዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.