Fana: At a Speed of Life!

የኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርቶች አውደ ርዕይ እና ባዛር በአዳማ ተከፈተ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 24 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርቶችን የሚያስተዋውቅ አውደ ርዕይ እና ባዛር በአዳማ ከተማ ተከፈተ፡፡

አውደ ርዕይ እና ባዛሩ የክልሉ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በተገኙበት በአዳማ ከተማ አባገዳ አዳራሽ ተከፍቷል፡፡

በወቅቱም የክልሉ አመራሮች፣ አርሶ እና አርብቶ አደሮች እንዲሁም የግብርናው ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

በአውደ ርዕይ እና ባዛሩ ላይም የተለያዩ የግብርና ምርቶች ቀርበዋል፡፡

የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳባ ደበሌ የፕሮግራሙ ዓላማ ለልምድ ልውውጥ፣ ለዘርፉ ዕድገት ድጋፍ ላበረከቱ ምሁራን እና ባለሀብቶች ዕውቅና መስጠት ነው ብለዋል፡፡

ክልሉ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ከውጪ የሚገባን ምርት በሀገር ውስጥ ለመተካት እና የግብርና ምርትን ወደ ውጪ በመላክ የውጪ ምንዛሪ ለማስገኘት እየሰራ መሆኑን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡

ፕሮግራሙ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል፡፡

በፕሮግራሙም የፓናል ውይይት የሚካሄድ ሲሆን ለግንባር ቀደም አርሶ እና አርብቶ አደሮች፣ ለዘርፉ እድገት በምርምር አስተዋጥዖ ላበረከቱ ምሁራን እና በክልሉ በግብርና ስራ ተሰማርተው ምሳሌ ለሆኑ ባለሀብቶች ዕውቅና እና ሽልማት ይሰጣል፡፡

በሙሉ ዋቅሹሜ

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳ
የፋና ድረ ቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.