Fana: At a Speed of Life!

የወራቤ ሆስፒታል የጥናት እና ምርምር ማዕከል እንዲሆን እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣የካቲት 17፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ)የወራቤ ኮምፕሬንሲቭ  ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የጥናት እና ምርምር ማእከል እንዲሆን እየተሰራ  መሆኑ ተገለጸ፡፡

የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጀማል ሽፋ ÷ በሆስፒታሉ የልብ፣የካንሰር እና የኩላሊት ህክምናዎችን ለመጀመር እንቅስቃሴ እየተደረገ  መሆኑን ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልጸዋል።

ሆስፒታሉ በቅርቡ የፕላስቲክ ቀዶ ህክምናን መስጠት መጀመሩን የጠቆሙት  ሃላፊው፥ ከዚህ በተጨማሪ ከአንገት በላይ ህክምና ፣ የአጥንት ህክምና፣ አጠቃላይ ቀዶ ህክምና፣ የስነ አዕምሮ እንዲሁም የህፃናት ህክምና በመስጠት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የሆስፒታሉን አሰራር በቴክኖሎጂ የማዘመን ስራ መጀመሩንም ጠቁመዋል።

በስልጤ ማህብረሰብ ወጭ በ 300 ሚሊየን ብር የተገነባው እና 5ኛ ዓመቱን የያዘው ሆስፒታሉ  584 አልጋዎችን   መያዙ ተገልጿል፡፡

በሆስፒታሉ በየቀኑ ከ 700 በላይ ታካሚዎች የሚስተናገዱ ሲሆን÷ በሳምንት ከ90 በላይ ትላልቅ የቀዶ ጥገና  ህክምናዎች የሚሰጡ መሆኑም ተመላክቷል።

በዙፋን ካሳሁን

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.