Fana: At a Speed of Life!

የዋጃ እና ጥሙጋ አካባቢዎች ከጁንታው ሕወሓት ነፃ ወጡ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትና እና የአማራ ልዩ ኃይል ከአላማጣ በቅርብ ርቀት የሚገኙትን  የዋጃ እና ጥሙጋን  አካባቢዎች መቆጣጠራቸው  ተገለጸ።

ከጽንፈኛ  ቡድኑ ነጻ ከወጡት ቦታዎች ባሻገር ቁጥራቸው በርከት የቡድኑ አባላት እጃቸውን እየሰጡ መሆኑም ተገልጿል።

የአካባቢው ነዋሪዎችምበ ፅንፈኛው የሕወሓት ቡድን ባለፉት ዓመታት ከፍተኛ ጭቆናበደል ሲደርስባቸው እንደነበር ገልፀዋል።

አሁን  ላይ በመከላከያ ሰራዊት፣ በአማራ ልዩ ኃይልና በሚሊሻ አባላት ከትህነግ ከሐዲ ቡድን ነጻ በመውጣታቸው ደስታቸውን እየገለጹ ነው።

የትግራይ ህዝብ የዘራፊውን ትህነግ ቡድን ሐገርን የማፍረስ ተግባር በመቃወም ከመንግስት ጎን መቆም እንዳለባቸውም መናገራቸውን አብመድ ዘግቧል።

#FBC

የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.