Fana: At a Speed of Life!

የዌልሱ ልዑል ቻርለስ በኮሮና ቫይረስ ተያዙ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 16 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የዌልሱ ልዑል ቻርለስ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተነገረ።

የ71 አመቱ ልዑል በተደረገላቸው ምርመራ በቫይረሱ መያዛቸውንና የቫይረሱ ምልክት እንደታየባቸው ከብሪታንያ ንጉሳዊ ቤተሰብ መኖሪያ የወጡ መረጃዎች አመላክተዋል።

የ72 አመቷ ባለቤታቸው ግን ከቫይረሱ ነጻ ሆነዋል ተብሏል።

አሁን ላይ እርሳቸውና ባለቤታቸው በለይቶ ማቆያ ራሳቸውን አግልለዋልም ነው የተባለው።

በብሪታንያ ከ8 ሺህ በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን መረጃዎች ያመላክታሉ።

ምንጭ፦ ቢቢሲ

ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.