Fana: At a Speed of Life!

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር በትግራይ ክልል ያለው የሰብአዊ ድጋፍ ሁኔታ መሻሻል እያሳየ መሆኑን ተናገሩ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 18 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቤዝሊ በትግራይ ክልል ያለው የሰብአዊ ድጋፍ ሁኔታ መሻሻል እያሳየ መሆኑን ተናገሩ፡፡

ዳይሬክተሩ በትግራይ ክልል ካለው የዓለም ምግብ ፕሮግራም ቡድን ጋር መወያየታቸውን አስታውቀዋል፡፡

በዚህም አሁን ላይ በክልሉ ያለው ሰብአዊ ድጋፍ ሁኔታ መሻሻል አሳይቷል ነው ያሉት፡፡

ይሁን እንጅ አሁንም ቢሆን ተጨማሪ ገንዘብ እና ስራዎች እንደሚያስፈልጉ ጠቅሰዋል፡፡

አያይዘውም በክልሉ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች እርዳታ እንዲያገኙ ለማድረግ እየሰሩ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.