የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ400 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አፀደቀ
አዲስ አበባ ፣ መስከረም 22 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ400 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አፀደቀ፡፡
የገንዘብ ሚኒስቴር በትዊተር ገጹ እንዳስታወቀው ድጋፉ የከተማ ሴፍቲኔት ፕሮግራምን ለመደገፍ የሚውል ነው፡፡
ከዚህ ውስጥ 50 ሚሊየን ዶላሩ ስደተኞች በሚገኙበት አካባቢ እንዲሁም በኢትዮጵያ ለሚኖሩ ስደተኞች የስራ እድል ፈጠራ የሚውል መሆኑምም ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡