Fana: At a Speed of Life!

የዓለም የምግብ ፕሮግራም በትግራይ ክልል ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም የምግብ ፕሮግራም ዋና ስራ አስፈጻሚ ዴቪድ ቤስሊ በትግራይ ክልል ድጋፍ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቁ፡፡

ዋና ስራ አስፈጻሚው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ከተወያዩ በኋላ የዓለም ምግብ ፕሮግራም በክልሉ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች የሚያደርገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡

ከዚህ ጋር ተያይዞም ለድጋፉ 107 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ያስፈልጋልም ነው ያሉት፡፡

በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ የዓለም ምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ ወዳጅ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.