Fana: At a Speed of Life!

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ 2 ሺህ 93 ተማሪዎችን አስመረቀ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 27 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 93 ተማሪዎች አስመረቀ።

በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ የብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት የፖለቲካና የሲቪክ አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊና የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር አለሙ ስሜ ተመራቂዎች በሰለጠኑበት ሙያ ለሀገራቸው ብልፅግና እንዲሰሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።

አያይዘውም ኢትዮጵያ በቀጣይ የምታከናውነው ምርጫ ነፃና ፍትሃዊ ሆኖ ይጠናቀቅ ዘንድ ተመራቂዎች የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ኡባህ አደም በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማር ሂደቱ ጎን ለጎን በማህበረሰብ አገልግሎት ላይ መሠማራቱን ገልፀዋል፡፡

ለዚህም ለማህበረሰቡ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱት ድምፃዊ አሊ ቢራን ጨምሮ ለበርካቶች የክብር ዶክትሬት መስጠቱን ለአብነት አንስተዋል።

የዛሬ ተመራቂ ተማሪዎችም በተማሩበት የትምህርት ዘርፍ ማህበረሰቡን እንዲያገለግሉ መልክታቸውን አስተላልፈዋል።

በእዮናዳብ አንዱዓለም

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.