Fana: At a Speed of Life!

የገቢዎች ሚኒስቴር አመራሮች እና ሰራተኞች የደም ልገሳ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 1፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በትግራይ ክልል ህግ በማስከበር ዘመቻ ላይ የሚገኙ የመከላከያ ሰራዊትን እና ለሌሎች ፀጥታ አካላትን ለመደገፍ የገቢዎች ሚኒስቴር አመራሮች እና ሰራተኞች የደም ልገሳ እያደረጉ ይገኛል::

ከ200 በላይ የተቋሙ ሰራተኞች በበጎ ፍቃድ ደም የለገሱት በግዳጅ ላይ ለሚገኙ የፀጥታ አካላት ከጎናቸው መሆናቸውን ለማሳየት በማለም መሆኑን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በሰጡት አስተያየት ገልፀዋል::

የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው እንደተናገሩት የሀገርን ሉዓላዊነት እና ክብር በማስጠበቅ ህግ በማስከበር ላይ ለሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት በዚህ ወቅት ደም በመለገስ አጋርነትን በተግባር ለማሳየት የልገሳ መርሃ ግብር መከናወኑን ተናግረዋል::

ደም መለገስ የህይወት ስጦታ በመሆኑ ህይወቱን ሳይሳሳ ለሀገሩ ለመክፈል ከተሰለፈው ጀግና ሰራዊት ጎን በዚህ ተግባር አጋርነትን በማሳየት አብሮ መቆም ይገባልም ብለዋል ሚኒስትሩ::

ደም እየለገሱ የሚገኙት ሰራተኞችም መንግስት በአጥፊው የህወሃት ቡድን ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ እንደሚደግፉ ገልፀዋል::

መላው የኢትዮጵያ ህዝብም በሚችለው ሁሉ ከፀጥታ ሀይሉ ጎን እንዲሰለፍም ጥሪ አቅርበዋል።

በመለሰ ምትኩ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.