የገንዘብ ሚኒስቴር እና የዓለም ባንክ የ300 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ
ባንኩ የዛሬ ወር በኢትዮጵያ በግጭት ምክንያት የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት ለተዘጋጀ ፕሮጀክት የሚውል የ300 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ ማፅደቁ የሚታወስ ነው።
በተለይም ድጋፉ የመሰረታዊ አገልግሎት አቅርቦትን ለማሻሸል እና ለዓየር ንብረት ለውጥ የማይበገር መሰረተ ልማት ለመገንባት እና በግጭት የተጎዱ የህብረተሰብ ክፍሎችን እንደሚያስቀድም ነው ባንኩ ያመለከተው።
በአጠቃላይ ድጋፉ ከ5 ሚሊየን የሚበልጡ ሰዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግም የባንኩ መረጃ ያመላክታል።
ውጤታማ እና ፈጣን ምላሽ ለመስጠትም በማሰብ የገንዘብ ድጋፉ በፌደራል መንግስት፣ በክልል መንግስታት እና በአካባቢዎቹ በሚንቀሳቀሱ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች በኩል እንደሚቀርብም ገልጿል።