Fana: At a Speed of Life!

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደግንባር መዝመት ለአፋር ህዝብ ትልቅ መልዕክት አለው – አይሻ መሀመድ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ወደግንባር መዝመት ለአፋር ህዝብ ትልቅ መልዕክት እንዳለው የመስኖ እና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መህመድ ገለጹ፡፡

ሚኒስትሯ “የአፋር ተጋድሎ እና አገር የማዳን ጥሪ” በሚል ርዕስ ጉደይ ዙሪያ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡

በቆይታቸውም የአፋር ህዝብ የጠቅላይ ሚኒስትሩን መዝመት ኢትዮጵያ መሪ የሚዘምትላት አገር መሆኗን ይበልጥ የተረዳበት እንደሆነ አንስተዋል፡፡

የአፋር ህዝብ አሸባሪው የህወሓት ቡድን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመቅበር ከሌሎች ወንድም ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን መነሳቱን ገልጸዋል፡፡

ወራሪው ቡድን በክልሉ በሴቶች፣ ህጻናት፣ ሃይማኖት አባቶች ላይ ያደረሰውን ጥፋት ገልጸው÷የአፋር ህዝብ አሸባሪውን ቡድን አይቀጡ ቅጣት እየቀጣው መሆኑንም ኢንጂነር አይሻ ጠቁመዋል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.