Fana: At a Speed of Life!

የፌዴራል እና የደቡብ ክልል የስራ ኃላፊዎች በጋሞ ዞን ጨንቻ ዙሪያ ወረዳ ዶርዜ ከተማ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 19፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌዴራል እና የደቡብ ክልል የስራ ኃላፊዎች በጋሞ ዞን ጨንቻ ዙሪያ ወረዳ ዶርዜ ከተማ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው፡፡

የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ፣ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እርስቱ ይርዳ፣ የደቡብ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጥላሁን ከበደ እና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው፡፡

ለልኡካን ቡድኑ የሰላም አምባሳደር የሆኑት የጋሞ አባቶች እርጥብ ሳር በመያዝ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.