Fana: At a Speed of Life!

የ2021 የኬሚስትሪ ኖቤል ሽልማትን ሁለት ሣይንቲስቶች በጋራ አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)በስዊድን ስቶኮልም “ሮያል ሣይንስ አካዳሚ” የተሰየመው የኖቤል ሽልማት ጉባዔ የ2021 የኬሚስትሪ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ለጀርመናዊው ሣይንቲስት ቤንጃሚን ሊስት እና ለአሜሪካዊው ዴቪድ ማክሚላን በጋራ ሸለመ፡፡

የኖቤል ኮሚቴው ÷ ሣይንቲስቶቹ የተሸለሙት በፋርማሲ ውስጥ በሚደረጉ ጥናቶች ለሞለኪውል ግንባታ ሲውል የነበረ “ኦርጋኖ ካታሊሲስ” የተሰኘ ትክክለኛለቱ ከፍተኛ የሆነ አዲስ ቁስ በማበልፀጋቸው ነው ብሏል፡፡

ሁለቱም ሳይንቲስቶች ዕድሜያቸው 53 ሲሆን÷ ለሽልማት የቀረበላቸውን 1 ነጥብ 1 ሚሊየን ዶላር ለሁለት እንደሚካፈሉ ነው የተገለጸው፡፡

ማክሚላን አሜሪካ ውስጥ በሚገኘው ፕሪንስተን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ፕሮፌሰር ሆኖ እያገለገለ የሚገኝ ሲሆን÷ ሊስት ደግሞ በጀርመን ማክስ ፕላንክ ኢንስቲትዩት ውስጥ በዳይሬክተርነት እየሠራ መሆኑን ሲጂቲኤን ዘግቧል፡፡

በዓለማየሁ ገረመው

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.