Fana: At a Speed of Life!

ጠ/ሚ ዐቢይ ለዓለም የምግብ ፕሮግራም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ምስጋና አቀረቡ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለዓለም የምግብ ፕሮግራም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዴቪድ ቢስሊ ምስጋና አቀረቡ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዋና ስራ አስፈጻሚው በኢትዮጵያ ያለውን የሰብአዊ እርዳታ ፍላጎት አስመልክቶ ላደረጉት ገንቢ አስተዋጽኦ እና ተጨባጭ ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

የዓለም የምግብ ፕሮግራም በኢትዮጰያ የሚያከናውነው ሥራ የሚደነቅ እና ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባው መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከዓለም ምግብ ፕሮግራም ዋና ስራ አስፈጻሚ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸው የሚታወስ ነው፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.