ጠ/ሚ ዐቢይ ሶስት የሚኒስትርነት ሹመቶችን ሰጡ
አዲስ አበባ፣ ጥር 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሶስት አዳዲስ የሚኒስትርነት ሹመቶችን ሰጡ።
በዚህም ዶክተር ኢንጅነር ጌታሁን መኩሪያ የትምህርት ሚኒስትር፣ አቶ መላኩ አለበል የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር እና ዶክተር አብርሃም በላይ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሆነው ተሾመዋል።
ሚኒስትሮቹ ከጥር 6 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ መሾማቸውን ኢቢሲ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤትን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።