Fana: At a Speed of Life!

ፋሲል ከነማ ለጠለምትና አዲአርቃይ ተፈናቃይ ወገኖች ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ፋሲል ከነማ ለጠለምትና አዲአርቃይ ተፈናቃይ ዜጎች ድጋፍ አድርጓል፡፡

ፋሲል ከነማ ከአዲአርቃይና ጠለምት አካባቢዎች በህልውና ማስከበር ዘመቻው ምክንያት በደባርቅ ከተማ በጊዜያዊነት ለተጠለሉ ከ16 ሺህ በላይ ወገኖች የልብስና የምግብ ቁሳቁስ ነው ድጋፍ ያደረገው፡፡

ድጋፉን ያበረከቱት የፋሲል ከነማ ደጋፊዎች ማህበር ፕሬዚደንት ወጣት ሃይለማርያም ፈረደ ÷ ለወገኖቻችን ለጊዜው ይሆን ዘንድ ከ600 ሺህ ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡

ከዚህ በፊትም በጋይንት ግንባር ለተሰለፈው የሃገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ እንዲሁም ፋኖ ድጋፍ ማድረጋቸውን አስታውሰዋል፡፡

የክለቡ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አብዮት ብርሃኑ ወገኖቻችን በችግር ላይ ሆነው ቆመን መመልከት የለብንም ብለዋል፡፡

ድጋፉ ከክለቡ ተጫዋቾች፣ የስታፍ አባላት እና ደጋፊዎች መሰብሰቡን ከሰሜን ጎንደር ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በቀጣይም ይህ የህልውና ዘመቻ እንኪጠናቀቅና ወገኖቻችን ወደ ቀያቸው እስኪመለሱ ድረስ ለማገዝ ዝግጁ ነን ብለዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.