Fana: At a Speed of Life!

ፌስቡክ መቀመጫቸውን ግብጽ አድርገው ኢትዮጵያ ላይ አነጣጥረው መረጃ ሲያሰራጩ ነበር ያላቸውን አካውንቶች ዘጋ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 30 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ፌስቡክ መቀመጫቸውን ግብጽ አድርገው ኢትዮጵያን ጨምሮ ሱዳን እና ቱርክን ኢላማ አድርገው መረጃ ሲያሰራጩ ነበሩ ያላቸውን አካውንቶች መዝጋቱን አስታወቀ።
አካውንቶቹ ከ300 ሺህ በላይ ተከታዮች እንዳላቸውም ነው ኩባንያው የገለጸው።
በዚህም ኩባንያው 17 የፌስቡክ አካውንት፣ 6 ገጾችና እና 3 የኢንስትግራም አካውንቶችን መዝጋቱን ነው የገለጸው።
ኩባንያው ባደረገው ምርመራ የፌስቡክ እና ኢንስታግራም ገጾቹ መቀመጫውን ግብፅ ያደረገ ቢ ኢንተራክቲቭ የተባለ ማርኬቲንግ ኩባንያ አካል መሆናቸውንም ነው ያስታወቀው።
ኩባንያው አክሎም አካውንቶቹ ሲያሰራጩ የነበረው በኢትዮጵያ በስፋት በሚነገው አማርኛ ቋንቋ ነው ሲል ገልጿል።
ይዘቱም ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ በገነባችው ግዙፍ ግድብ ላይ ያነጣጠረ ነው ብሏል።
ምንጭ፡-ቢቢሲ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡-

https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
No photo description available.
0
People Reached
115
Engagements
Boost Post
99
5 Comments
11 Shares
Like

 

Comment
Share
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.