Fana: At a Speed of Life!

ፌስቡክ ከሶስት የአውስትራሊያ መገናኛ ብዙሃን ጋር ለሚያጋሩት ዜና ገንዘብ ለመክፈል ተስማማ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 19፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ፌስቡክ ከሦስት የአውስትራሊያ መገናኛ ብዙሃን ጋር በገጹ ላይ ለሚያጋሩት ዜና ገንዘብ መክፈል የሚያስገድደውን ስምምነት ተፈራረመ፡፡

የአውስትራሊያ ፓርላማ እንደፌስቡክ ያሉ የቴክኖሎጅ ኩባንያዎች ተጠቃሚዎች በገጻቸው ላይ ለሚያጋሩት ዜና ገንዘብ እንዲከፍሉ የሚያደርግ ህግ አጽድቋል፡፡

ይህን ተከትሎም የፌስቡክ ኩባንያ ከሶስት የአውስትራሊያ የግል መገናኛ ብዙሃን ጋር ስምምነቶችን ፈርሟል፡፡

ስምምነቱ የሚዲያ አውታሮቹ በገጻቸው ለሚያጋሩት ዜና ፌስ ቡክ ገንዘብ እንዲከፍል የሚያደርገው ነው፡፡

ፌስቡክ የአውስትራሊያ ተጠቃሚዎች ዜና እንዳይመለከቱ ወይም እንዳያጋሩ ከሳምንት በፊት እግድ መጣሉ የሚታወስ ሲሆን፤ ኩባንያው እገዳውን አንስቶ ስምምነቱን መቀበል ግድ ሆኖበታል፡፡

አውስትራሊያ ያወጣችውን ድንጋጌ ሲኮንን እና ሲቃወም የነበረው የመረጃ ማፈላለጊያው ገጽ ጎግል የተባለውን ክፍያ ለመክፈል መስማማቱ የሚታወስ ሲሆን፤ ፌስቡክም የሃገሪቱን ህግ በመቀበል ስምምነት ፈጽሟል፡፡

በዚህም ሃገሪቱ የቴክኖሎጅ ኩባንያዎች ተጠቃሚዎች በገጻቸው ላይ ለሚያጋሩት ዜና ገንዘብ እንዲከፍሉ በማድረግ ቀዳሚ ሆናለች፡፡

ሆኖም የስምምነቱ የፋይናንስ ዝርዝር ግልጽ አለመደረጉን መረጃው አንስቷል፡፡

ምንጭ፡- አልጀዚራ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.