Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚደንት ሣህለ ወርቅ ከካናል ፕላስ ግሩፕ የአፍሪካ ማናጀር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 4፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)ፕሬዚደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ በቴሌቪዥን ኢንደስትሪው ግንባር ቀደም ከሚባሉት መካከል የሚመደበው የካናል ፕላስ ግሩፕ የአፍሪካ ማናጀር ጋር ተወያይተዋል::

በመዝናኛው የቴሌቪዥን መስክ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ እና ጥሩ የሚባሉ አዝናኝ እና አስተማሪ ፕሮግራሞችን በማቅረብ ዝነኛ የሆነው ካናል ፕላስ በኢትዮጵያም ፅህፈት ቤት በመክፈት ስራ መጀመሩን ስራ አስኪያጁ አብራርተዋል::

ፕሬዚደንት ሣህለ ወርቅ ካናል ፕላስ ኢትዮጵያዊ ለዛና ጣዕም ያላቸው ዝግጅቶችን በመርሀ ግብሩ ማካተቱን አድንቀዋል::

መርሃግብሮቹን ለመዝናኛነት ብቻ ሳይሆን ለማስተማሪያነትም መጠቀም አስፈላጊ መሆኑን አፅንኦት መስጠታቸውንም ከፕሬዚደንት ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል::

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.