Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ ለሚያደርጉት የስራ ጉብኝት ጅማ ገብተዋል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 2፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ ለሶስት ቀናት የስራ ጉብኝት ለማድረግ ጅማ ከተማ ገብተዋል።

ፕሬዚዳንቱ ጅማ አባ ጅፋር አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋርም የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳልህ እና አማካሪያቸው የማነ ገብረዓብ ኢትዮጵያ ገብተዋል።

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በሁለትዮሽ ግንኙነትና የቀጠናው ሀገራት ትስስር ላይ እንደሚወያዩ የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል በትዊተር ገፃቸው አስፍረዋል።

የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.