ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በጅማና ዳውሮ ጉብኝት አድርገዋል
አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በጅማ እና ዳውሮ ጉብኝት አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጅማ አባ ጅፋር አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም በአባ ገዳዎች፣ በሀይማኖት አባቶች የሀገር ሽማግሌዎች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ተወካዮች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
በአቀባበሉ ላይም ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ለሌሎችም እንግዶች የተለያዩ ስጦታዎች እንደተበረከቱም ከጅማ ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከውጭ ሀገራት ባለሀብቶች ጋር በመሆን በደቡብ ክልል ዳውሮ ዞንም ጉብኝት አድርገዋል።