Fana: At a Speed of Life!

60 የትምህርት አይነቶችን A+ በማምጣት ታሪክ የሰራው የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ የዘንድሮ ተመራቂ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ 2014 ዓ.ም የፊዚክስ እና የሂሳብ ትምህርት ተመራቂው ራጂ አሸናፊ 60 የትምህርት አይነቶችን A+ በማምጣት ታሪክ ሰርቷል፡፡

አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መስኮች ሲያሰለጥናቸው የቆዩ 1 ሺህ 253 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡

የ25 አመቱ ወጣት ራጂ በአዳማ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የዘንድሮው አመት የፊዚክስ እና የሂሳብ ትምህርት ተመራቂ ሲሆን በ60 የትምህርት አይነቶች A+ በማምጣት አስገራሚ ውጤት አስመዝግቧል፡፡

ራጂ ተወልዶ ያደገው ቄለም ወለጋ ጊዳሚ ከተማ ሲሆን የ10ኛ ክፍል ውጤቱ በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች A እንደነበር እና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤቱም 647 እንደነበር ተገልጿል፡፡

በዓለም ላይ ካሉት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ግንባር ቀደም የሆነው ኤም አይ ቲ ራጂ እስከ ፒ ኤች ዲ ድረስ በዩኒቨርሲቲው ተቀላቅሎ እንዲማር ነጻ የትምህርት እድል ለመስጠት ቃል እንደገባላቸውም የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ለሚ ጉታ ተናግረዋል፡፡

በረጋሳ ፍሮምሳ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.