Fana: At a Speed of Life!

773 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ13 ሰዎች ህይወት አልፏል

አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 4 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት 24 ሰአታት ለ11 ሺህ 39 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 773 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ፡፡

ሚኒስትሯ በፌስ ቡክ ገጻቸው ባወጡት መረጃ ባለፉት 24 ሰአታት የ13 ሰዎች ህይወት ማለፉንም አስታውቀዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም ባለፉት 24 ሰአታት 205 ሰዎች ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይም 10 ሺህ 411 ሰዎች ከቫይረሱ አገግመዋል፡፡

እንዲሁም 164 ሰዎች በፅኑ ህክምና ላይ ይገኛሉም ነው ያሉት፡፡

በኢትዮጵያ እስካሁን ለ509 ሺህ 10 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 23 ሺህ 591 ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል፡፡

ከዚህ ውስጥ 10 ሺህ 411ዱ ያገገሙ ሲሆን 12 ሺህ 758 ሰዎች ደግሞ ቫይረሱ ይገኝባቸዋል፡፡

እንዲሁም 420 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ሳቢያ ለህልፈት ተዳርገዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.