የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ በቴል አቪቭ በተካሄደ የቱሪዝም ዐውደ ርዕይና ኮንፈረንስ ላይ ተሳተፈች

By Tibebu Kebede

February 13, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ በእስራኤል ቴል አቪቭ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ዐውደ ርዕይና ኮንፈረንስ ላይ ተሳተፈች።

የቱሪዝም ዐውደ ርዕይና ኮንፈረንሱ “ዓለም አቀፍ የሜዲትራኒያን የቱሪዝም ገበያ 2020” በሚል መሪ ቃል ከየካቲት 3 እስከ የካቲት 4 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ መካሄዱን በእስራኤል የኢትዮጵያ ኤምባሲ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት መላከው መረጃ አመላክቷል።