አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ በእስራኤል ቴል አቪቭ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ዐውደ ርዕይና ኮንፈረንስ ላይ ተሳተፈች።
የቱሪዝም ዐውደ ርዕይና ኮንፈረንሱ “ዓለም አቀፍ የሜዲትራኒያን የቱሪዝም ገበያ 2020” በሚል መሪ ቃል ከየካቲት 3 እስከ የካቲት 4 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ መካሄዱን በእስራኤል የኢትዮጵያ ኤምባሲ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት መላከው መረጃ አመላክቷል።