የሀገር ውስጥ ዜና

አዲሱ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ ቁጥጥር እየተደረገ ነው – የጤና ሚኒስቴር

By Feven Bishaw

December 01, 2021

 

አዲስ የኮቪድ 19  ዝርያ  በመምጣቱ  በርካታ የአለም ሃገራት በወረርሽኝ እየተመቱ በመሆኑ  ክትባቱን መውሰድ አስፈላጊ መሆኑን ያሳሰቡት ሚኒስትሯ  ÷ ባለፉት ሁለት ሳምንት እየተሰጠ በሚገኘው የክትባት ዘመቻ  እስካሁን ከ4 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ የክትባት ዶዝ መስጠት ተችሏል   ብለዋል፡፡

አዲስ የኮቪድ 19  ዝርያ የሆነውን “የኦሚክሮን” ቫይረስ ለመከላከል በመግቢያ በሮችና በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል የነበሩ ቁጥጥሮችን  የማጥበቅ ስራ እየተሰራ  መሆኑን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ እስካሁን ከ6 ሺህ 700 በላይ ሰዎች በቫይረሱ ሳቢያ ህይወታቸው አልፏል።